What Guides Us

What We Believe

Our statement of faith outlines the core biblical truths that guide our worship, ministry, and collective lives.

14 CORE DOCTRINES
01
መጽሐፍ ቅዱስ

The Authority of the Bible

ስድሳ ስድቱን የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻህፍት የያዘውን መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር እስትንፋሳ ቃል፣ ምንም ስህተት የማይገኝበት ፣ እምነትን እና ተግባርን በሚመለከት ሁሉ የመጨረሻው ሥልጣን ያለው ፣ህያው እና ዛሬም የሚሰራ ፣ እንደ ሆነ እናምናለን፡፡

02
ሥላሴ

The Holy Trinity

በእግዚአብሔር አብ፣ በእግዚአብሔር ወልድ፣ በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ፣ አንድ አምላክ ፣እናምናለን፡፡

03
የእግዚአብሔር የበላይነት

The Sovereignty of God

በመፍጠር ስራ፣ ፍጥረትን በመጠበቅ ፣ በመገለጥ ፣በመዋጀት እና በመጨረሻው ፍርድ የእግዚአብሔርን ፍፁም ሥልጣን እና የበላይነት እናምናለን፡፡

04
ኢየሱስ ክርስቶስ

Jesus Christ

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከአብ የተላከ መሆኑን ፣ በመንፈስ ቅዱስ መፀነሱን ፣ ከድንግል ማርያም መወለዱን ፣ፍፁም ሰው ፍፁም አምላክ መሆኑን ፣ ለሰው ልጃች ቤዛ ሆኖ በመስቀል ላይ መሞቱን ፣ መቀበሩን፣ በሶስተኛው ቀን በአካል ከሙታን መነሳቱን፣ ወደ አብ ማረጉን እና አሁንም በአብ ቀኝ ሆኖ ስለ እኛ እንደሚማልድ ፣ ደግሞም በህያዋንና በሙታን ላይ ሊፈርድ በክብርና በግርማ እንደሚመለስ እናምናለን፡፡

05
መንፈስ ቅዱስ

The Holy Spirit

መንፈስ ቅዱስ የመለኮት ባሕርያት ሁሉ ያሉት ፍጹም አምላክ እንደሆነ እና አምልኮ እና ስግደት እንድሚገባው እናምናለን፡፡

06
የሰው መውደቅ

The Fall of Man

ሰው በእግዚአብሔር አምሳል መፈጠሩን ፣ በኃጥያት መውደቁን እና በዚህም ምክንያት የእግዚአብሔር ቁጣና ፍርድ ያለበት በደለኛ መሆኑን እናምናለን፡፡

07
መዳን በፀጋ

Salvation by Grace

ሰው ከኃጢአት ዕዳ ፣ ኃይልና ቅጣት ፣ ሊድን የሚችለው ኃጥያት የለለበት የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ የሰው ምትክ ሆኖ በፈጸመው የቤዛነት ስራ ብቻ በመሆኑ ኃጥያተኛ በእግዚአብሔር ፀጋ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን ብቻ እንደሚጽድቅ እናምናል፡፡

08
ዳግመኛ መወለድ

Regeneration

ኃጥያተኛ በኃጥያቱ ተፀጽቶ ንሰሐ እንዲገባ ፣ በኢየሱስ ክርስቶስ አምኖ ዳግመኛ በመወለድ አዲስ ፍጥረት እንዲሆን መንፈስ ቅዱስ በህይወቱ እንሚሰራ እናምናልን፡፡

09
የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት

Baptism in the Holy Spirit

መንፈስ ቅዱስ በአማኝ ህይወት ውስጥ እንደሚኖር ፣ አማኙ በመንፈስ ቅዱስ ሲጠመቅ ኃይልን እንደሚቀበልና በልሳን እንደምናገር በየጊዜውም በመንፈስ ቅዱስ እንደሚሞላ እናምናለን፡፡

10
መንፈሳዊ ስጦታዎች እና ተዐምራት

Spiritual Gifts & Miracles

መንፈስ ቅዱስ ዛሬም ቤተ ክርስቲያንን ለማነጽ ለአማኞች ልዩ ልዩ የጸጋ ስጦታዎችን በማካፈል፣ድውዮችን በመፈወስ ፣ አጋንትን በማውጣትና ፣እና ተዐምራትን በማድረግ እንመድሰራ እናምናለን፡፡

11
የቤተ ክርስቲያን ተልዕኮ

The Mission of the Church

ቤተ ክርስቲያን በክርስቶስ የተሰጣትን የታላቁን ተልዕኮ አደራ በመወጣት ወንጌልን ለሰዎች ሁሉ እንድትሰብክ እና አማኞች ደቀ መዛሙርት በማድረግ ለክርስቶስ አካል መታነጽ አስፈላጊውን ሁሉ መፈጸም እንደምትችል መንፈስ ቅዱስም ሐዋርያትን፣ ነቢያትን፣ ወንጌል ሰባኪዎችን ፣እረኞችን እና አስተማሪዎችን እንዲሁም ሌሎች የአገልግሎት ስጦታዎችን እንደሚሰጥ እናምናለን፡፡

12
አንዲት ቅድስት ቤተክርስቲያን

One Holy Church

ከእግዚአብሔር መንፈስ ዳግም የተወለዱ ሁሉ በሚገኙባት፣ የክርስቶስ አካል በሆነች፣ በአንዲት ቅድስት ቤተክርስቲያን እናምናለን፡፡

13
ጥምቀትና የጌታ እራት

Baptism & The Lord's Supper

ጌታችን እና መድኅንታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ባዘዘው መሰረት ፣ዳግም የተወለደ አማኝ ከክርስቶስ ሞት እና ትንሳኤ ጋር መተባበሩን እንዲሁም ለኃጥያት መሞቱን እና ለጽድቅ መነሳቱን ለመግለጽ በአብ, በወልድ, እና በመንፈስ ቅዱስ ስም በውኃ ውስጥ በመጥለቅ እንዲጠመቅ እንዲሁም ጌታ ዳግም እስኪመጣ ሞቱን ለመናገርና , ከጌታ እና ለአማኞች ጋር ያለውን ኅብረት ለመግለጽ የጌታ እራት እንደሚካፈል እናምናለን፡፡

14
የዘላለም ህይወትና ፍርድ

Eternal Life & Judgment

በሙታን ትንሳኤ፣ በኃጥያተኞች ላይ በሚደርሰው የዘላለም ፍርድና አማኞች በሚቀበሉት የዘላለም ህይወት እናምናለን፡፡

CONNECT WITH US

Questions of Faith?

Our pastoral team is available to walk through any questions about our statement of faith.

Contact Pastoral Team